Tuesday, May 5, 2020

ኪርያላይሶን ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ

ልደታ ደብረ መድኅኒት መድኃኔዓለም አዲስ አበባ።

ኪርያላይሶን/8/
°°°°
እስቲ ላስታውሰው ጌታዬን
በማዘን በማልቀስ
ለሰው ሲል የሞተ
የማይሞተው ንጉሥ
ሲከሰስ በአውደ ጲላጦስ ስብሐት ለከ
°°°°
ያ አንደበትህ ጣፋጭ
ለምጽና አንካሳ የሚፈውስ
በጲላጦስ ተጠየቀ እንዲሰጥ የቃል መልስ
የእኛ ሥራ አበቃህ ለክስ ወዮ ወዮ
°°°°
እነዚያ ቅዱሳን እጆችህ
ዓለሙን ሁሉ የሰሩ
ተዓምራት በማድረግ እውራን ያበሩ
በመስቀል ላይ ተቸነከሩ ስብሐት ለከ
°°°°
ኃጢአትን ለመደምሰስ እግሮችህ በዮርዳኖስ የገቡ
እንደ ወንጀለኛ ሆኑ በጲላጦስ ፊት
በእኛ ጥፋት ስለኛ ኃጢአት አቤት አቤት
°°°°
ከላይ ከሰማያት ወርደህ
የሰው ልጅ ፍቅር አስገድዶህ
ፍዳና መከራ ስቃይን ተቀበለክ
በዘጠኝ ሰዓት ነፍስህ ሰጠህ አንተም ተፈጸመ አልክ
     
   
 ምንጩ የዚሁ ብሎግ አዘጋጅ እዚህ በመጫን ድምጹን ይስሙ : http://t.me/orthodoxzema
      

No comments:

Post a Comment