Thursday, April 30, 2020

ጻድቁ ተክለሃይማኖት በጸሎት እግሩ እንደተሰበረች በቅኔ


መነነቶ ወኅደገቶ
ለተክለሃይማኖት አብ ጽኑዓ ሃይማኖት መሐላ
ብእሲት እግሩ ዘዓቢይ ኅይላ
ወኢፈቀደት ነቢረ ውሳጤ ቀዊም መርጡላ
ስድስተ አክናፈ ደቂቀ ተድላ
በላዕሌየ ወለደ ብሂላ
#ትርጉም: ሃይሏ ትልቅ የሆነ እግሩ/ሴት የሀይማኖት መሃላን ያጠና ተክለሃይማኖትን ናቀችውና ተወችው። ስድስት ክንፎችን/የምቾት ልጆችንም በላዬ ወለደ ብላ በመቆሚያ ቤቷ ውስጥ መኖርን አልወደደችም።
#ትንታኔ፡ የጎልማሳ ሚስት ባልዋ በላይዋ ላይ ከሌላ ሴት ልጅ ከወለደ ትታው እንደምትለየው ሁሉ ጻድቅ ተክለሃይማኖትም ሰባት ዓመት ቆመው  ሲጸልዩ አንድ እግራቸው ተሰብሮ ስድስት የጸጋ ክንፎች አገኙ ይላሉ ባለቅኔው።
ባለቅኔው መሪጌታ ያሬድ ዘቂርቆስ

No comments:

Post a Comment