Friday, May 1, 2020

የድንግል ማርያም ምልጃ በቅኔ

ተዘከር ወልድ ፍተ ርህራሄከ እክል
እስመ ቅድመ ገጽከ ቆመት ሰዓሊተ ምህረት ድንግል
ትርጉም:
ወልድ የርህራሄ እህል ቁራሽን ተዘከር(አስብ)
ምህረትን ለማኝ በፊትህ ቆማለችና
ትንታኔ:
እንጀራ የምትለምን ሴት ቁራሽ ተዘከሯት እንደሚባል ወልድ ሆይ ለእናትህ የሰጠሃትን ቃልኪዳን አስበህ በፊትህ ቆማ ስትማልድ ራራ ይላሉ ባለቅኔው።
(ባለቅኔው )አለቃ ወልደማርያም ሀብቱ



No comments:

Post a Comment